6133 0115533852 / 0935947533Kazanchiz Addis Ababa, Ethiopia

የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ቢሾፍቱ ሥልጠና ማዕከል የመኝታ ክፍሎች እድሳት ዉስን ጨረታ ግዥ ሂደት በተካሄደ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል ጥናት ሪፖርት ላይ ውይይት ተካሄደ

የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ቢሾፍቱ ሥልጠና ማዕከል የመኝታ ክፍሎች እድሳት ዉስን ጨረታ ግዥ ሂደት በተካሄደ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል ጥናት ሪፖርት ላይ ውይይት ተካሄደ

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጳጉሜን 5/2017 ዓ.ም) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ቢሸፍቱ የሥልጠና ማዕከል የመኝታ ክፍሎች እድሳት ለማከናወን በተካሄደ ውስን የጨረታ ግዥ ሂደት ላይ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል ጥናት አካሂዷል።

በጥናቱ ግኝቶች ላይም ከኢንስቲትዩቱ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሂዷል።

ጥናቱ ኢንስቲትዩቱ ጨረታውን በግልፅ ሳያወጣ ወደ ውስን ጨረታ መውሰዱን፣ የ መሀንዲስ ግምት ሳይሠራ በ45 ሚሊዮን ብር ይፈጸማል ተብሎ ህጋዊ አሠራርን ያልተከተለ ግምትን መነሻ በመውለድ ተጠይቆ የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ምላሽ ከተሰጠ በኋላ ሌላ የመሀንዲስ ግምት መሠራቱን አመልክቷል።

ኮሚሽኑ በጥናቱ የተለዩትን ግኝቶች ግድፈቶች መሠረት አድርጎ፣ በውስን ጨረታ የተፈጸመው የኮንስትራክሽን ግዥ የመንግሥት ግዥ አዋጅና የአሠራር መመሪያን ያልተከተለ እና ግልፅነት የጎደለው በመሆኑ፣ ጨረታው ተሰርዞ የተፈጸሙ ክፍተቶች ተስተካክለው በፍትሃዊና ግልፅ በሆነ መንገድ እንደገና ጨረታ እንዲወጣ ምክረ ሐሳብ አቅርቧል።

የኢንስቲትዩቱ አመራሮችም የቀረበውን የጥናት ምክረ ሀሳብ ተቀበለው ለመተግበር ተስማምተዋል።

ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገ ስብዕናን ይገነባል!

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

Related Posts

Leave a Reply