+251115579202 / 0953222255 / 0953222255Kazanchiz Addis Ababa, Ethiopia

ኢትዮጵያ በብሪክስ (BRICS) መድረክ አማካኝነት ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ትብብርን እያጠናከረች ነው

የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኢትዮጵያን በመወከል በሃይደራባድ፣ ህንድ በተካሄደው ሁለተኛው የBRICS ፀረ-ሙስና የሥራ ቡድን (ACWG) ስብሰባ ላይ በመሳተፍ ሙስናን ለመዋጋት በሚደረገው ዓለም አቀፍ ጥረት ውስጥ ያላትን ተሳትፎ አጠናክራለች።

የBRICS አባል ሀገራት እና አጋሮች የውይይት መድረክ ሙስናን በመከላከል እና በመዋጋት ረገድ የተጠናከረ ትብብርን ለመወያየት፣ የህግ አስከባሪ ትብብርን በማጠናከር፣ ከሙስና ጋር የተያያዙ ወንጀኞችን በመከታተል እና የርክክብ ሂደቶችን ለማመቻቸት በሚደረጉ ጥረቶች ላይ በማተኮር ውይይት ተካሂዷል።

በሥራ ቡድኑ የውይይት መድረክ ወቅት ኢትዮጵያ ሙስናን በመዋጋት እና የሥነምግባር ግንባታን በማስተዋወቅ ረገድ ያላትን ተሞክሮ እና ቀጣይ እርምጃዎችን አጋርታለች። ይህም ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ አጋርነት አማካኝነት በሙስና ላይ የጋራ እርምጃ ለመውሰድ ያላትን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳያል።

ኢትዮጵያን ወክለው በስብሰባው ላይ የተሳተፉት የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቱ አስፋው ኢትዮጵያ ሙስናን ለመከላከል እና ለመታገል የምታደርገውን ጥረት እና ያሏትን ተሞክሮዎችና ለፀረ-ሙስና ትግሉ የመንግስትን ቁርጠኝነት በመድረኩ ያቀረቡ ሲሆን፤ በብሪክስ ማዕቀፍ ውስጥ አብሮ ለመስራት ያላትን ቁርጠኝነትም አረጋግጠዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎቹም የBRICS መደበኛ ያልሆነ ትብብር ማዕከል ማቋቋም እና ከሙስና ጋር የተያያዙ ወንጀሎችን ለመወጣት ኃላፊነት ባላቸው ተቋማት መካከል ቅንጅትን ለማሻሻል የህግ አስከባሪ ባለሙያዎች ኔትወርክ ማዘጋጀትን ጨምሮ የሥራ ተነሳሽነቶች ላይ ተወያይተዋል።

Related Posts