Category

News
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም) ለፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሴት አመራርና ሠራተኞች “የሴቶች ሚና በሥነምግባር ግንባታ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል። በመድረኩ የተገኙት በኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ ትውልድን በመልካም ሥነምግባር በማነጽ በኩል የሴቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው፤ ትውልድን በማስቀጠልና ሀገርን ወደ ብልፅግና ለማድረስም ድርሻቸው የጎላ ነው...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከዘርፍ ፎረም አመራሮችና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር የሥልጠና ጥራትና ተገቢነት ኮንፈረንስ አካሂዷል፡፡ ኮንፈረንሱ ባለትፉት 9 ወራት የተሰጡ ስልጠናዎች ምን ያህል ጥራትና ተገቢነታቸውን የጠበቁ ናቸው የሚለውን ለመገምገምና በቀጣይ የሚሰጡ ስልጠናዎች ላይ የጋራ አቅጣጫ ለማስቀጥ ነው፡፡ በኮንፈረንሱ ባለፉት ወራት ሲሰጡ የነበሩ ስልጠናዎች ዘርፍ...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ) የፌደራል የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከዘርፍ ፎረም አመራሮችና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር በ26 ዘርፎች በተጠኑ የአሰራር ሥርዓት ጥናቶች ላይና በዲጂታል የሀብት ምዝገባ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል። በመድረኩ የተገኙት በኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት ዘርፍ ም/ኮሚሽንር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው ባለፋት ዘጠኝ ወራት በሙስና መከላከል ሥራ ላይ ውጤታማ...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሚያዚያ 25/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከደቡብ ኮሪያ የፀረ-ሙስና እና ሲቪል መብቶች ኮሚሽን ጋር በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ዙሪያ በተፈራረሙት የጋራ ስምምነት መሰረት ለኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች የዓቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል። ስልጠናው የፀረ-ሙስና ህጎች ትግበራ፣ በተቋማት የጥቅም ግጭት መከላከል፣ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ እና የሀብት ምዝገባ መረጃ የማጣራት አፈጻጸም፣ የተቋማት ኃላፊዎች የሥነምግባር...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሚያዝያ 07/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በፌደራል ተቋማት የንብረት አያያዝና አወጋገድ አሰራር ሥርዓት ግልጽነት ላይ ያጠናውን ጥናት ለገንዘብ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች አቅርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። በውይይት መድረኩ የተገኙት በኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋው ኮሚሽኑ በትውልድ ሥነምግባር ግንባታ፣ በሙስና ቅድመ መከላከልና ህግ ማስከበር ላይ ትኩረት...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሚያዚያ 7/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌዴራል የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን “የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፤ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ!” በሚል መሪ ቃል በሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት መከላከልና ማስተዳደር ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ስልጠናዊ ውይይት ከቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ጋር አካሂዷል። በስልጠናዊ ውይይቱ ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር እንደገና አበበ ከፍተኛ አመሪሩ አርዓያ በመሆንና...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 29/2018 ዓ.ም) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራርና ሠራተኞች በ2018 በጀት ዓመት ባለፋት ዘጠኝ ወራት የሥራ ክፍሎች ውጤት አመልካች ተግባራት የእቅድ አፈፃፀም ላይ ግምገማዊ ውይይት አካሂደዋል። በግምገማዊ ውይይቱ በሙስና መከላከል ዘርፍ፦ የሙስና መከላከል ጥናት፣ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል እና የሀብት ምዝገባ እና ትክክለኛነት ማጣራት ሥራ ክፍሎች፤ በሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ፦ የፀረ-ሙስና የህዝብ ግንዛቤ ማጎልበቻ፣ የሥነምግባርና...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በመንግስት ሆስፒታሎች አገልግሎት አሰጣጥና ግልጽነት ላይ ያጠናውን ጥናት ለዘርፉ አመራሮች አቅርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። ጥናቱ በመንግስት ሆስፒታሎች ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ አሰራሮችን በመለየትና የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በውይይቱ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ መንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ‘‘የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፤ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ!’’ በሚል መሪ ቃል ከሰላም ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ዘርፍ-ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሂዷል። ስልጠናዊ ውይይቱ በዘርፉ የሚስተዋሉ ዋና ዋና የሙስና ሥጋት እና ተጋላጭነት መገለጫ የሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እና ሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት ማስተዳደር ዙሪያ ግንዛቤ ለመፍጠር ትኩረት ያደረገ...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ  መጋቢት 24/2018 ዓ.ም) የዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ስምምነት አስፈፃሚ የባለድርሻ ተቋማት አመራሮች እና የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካዮች የምክክር እና አቅም ግንባታ መድረክ ተካሄዷል። የመድረኩ ዓላማ የፀረ-ሙስና ስምምነቱ አስፈፃሚ ባለድርሻ ተቋማት በስምምነቱ መነሻ የተዘጋጀው አገራዊ የፀረ-ሙስና ትግል ማስፈጸሚያ ሕጎች፣ ስትራተጂ እና ተቋማዊ አቅም ያለበትን ሁኔታ ለመገምገም ነው። የተባበሩት መንግስታት የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽን (UNCAC) በዓለምአቀፍ ደረጃ ብቸኛው የፀረ-ሙስና ሰነድ ሲሆን፣...
Read More
1 2 3 4