Category

News
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 29/2018 ዓ.ም) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራርና ሠራተኞች በ2018 በጀት ዓመት ባለፋት ዘጠኝ ወራት የሥራ ክፍሎች ውጤት አመልካች ተግባራት የእቅድ አፈፃፀም ላይ ግምገማዊ ውይይት አካሂደዋል። በግምገማዊ ውይይቱ በሙስና መከላከል ዘርፍ፦ የሙስና መከላከል ጥናት፣ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል እና የሀብት ምዝገባ እና ትክክለኛነት ማጣራት ሥራ ክፍሎች፤ በሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ፦ የፀረ-ሙስና የህዝብ ግንዛቤ ማጎልበቻ፣ የሥነምግባርና...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በመንግስት ሆስፒታሎች አገልግሎት አሰጣጥና ግልጽነት ላይ ያጠናውን ጥናት ለዘርፉ አመራሮች አቅርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። ጥናቱ በመንግስት ሆስፒታሎች ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ አሰራሮችን በመለየትና የመፍትሔ ሀሳቦችን በማቅረብ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በውይይቱ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ መንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ‘‘የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፤ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ!’’ በሚል መሪ ቃል ከሰላም ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ዘርፍ-ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሂዷል። ስልጠናዊ ውይይቱ በዘርፉ የሚስተዋሉ ዋና ዋና የሙስና ሥጋት እና ተጋላጭነት መገለጫ የሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እና ሥነምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥና የጥቅም ግጭት ማስተዳደር ዙሪያ ግንዛቤ ለመፍጠር ትኩረት ያደረገ...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ  መጋቢት 24/2018 ዓ.ም) የዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ስምምነት አስፈፃሚ የባለድርሻ ተቋማት አመራሮች እና የቴክኒክ ኮሚቴ ተወካዮች የምክክር እና አቅም ግንባታ መድረክ ተካሄዷል። የመድረኩ ዓላማ የፀረ-ሙስና ስምምነቱ አስፈፃሚ ባለድርሻ ተቋማት በስምምነቱ መነሻ የተዘጋጀው አገራዊ የፀረ-ሙስና ትግል ማስፈጸሚያ ሕጎች፣ ስትራተጂ እና ተቋማዊ አቅም ያለበትን ሁኔታ ለመገምገም ነው። የተባበሩት መንግስታት የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽን (UNCAC) በዓለምአቀፍ ደረጃ ብቸኛው የፀረ-ሙስና ሰነድ ሲሆን፣...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 15/2018 ዓ.ም) 16ኛው አገርዓቀፍ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖች ትስስር ጉባኤ የመካከለኛ ዘመን ስትራቴጂክ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የቀጣይ ሶስት አመታት ስትራቴጂክ እቅድ ዝግጅት ላይ ግምገማዊ ውይይት ተካሂዷል። አገርዓቀፍ የትስስር ጉባኤው ባለፉት ሶስት አመታት በሥነምግባር ግንባታ፣ በሙስና መከላከል፣ በተቋማዊ ማስፈጸም አቅም ግንባታ ጋር በተያያዘ ለፀረ-ሙስና ትግሉ አጋዥና ቁልፍ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የጋራ ስምምነት በመፍጠር...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ መጋቢት 10/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የጋራ ተልዕኮ የሆነውን የሙስና ወንጀል መረጃ የማመንጨት እና የምርመራ መዝገብ ዝግጅት ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሁም ውጤታማነት ላይ የግምገማ መድረክ አካሂደዋል፡፡ በግምገማ መድረኩ የተገኙት የፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒ.ኤች.ዲ) ኮሚሽኑ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት ከዜጎች የሚቀርቡ የሙስና ወንጀል...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 24/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ‘‘የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፣ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ’’ በሚል መሪ ቃል ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ዘርፍ-ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሄዷል። በስልጠናዊ ውይይቱ ላይ የተገኙት የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አብረሃም በላይ (ዶ/ር)፤ ዘርፋችን ሰፊ ፕሮጀክቶችን እና ሀብትን የሚያስተዳድር በመሆኑ አመራሩ ሥነምግባርን የተላበሰ...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 24/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከትምህርት ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ዘርፍ-ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሂዷል። በስልጠናዊ ውይይቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአጠቃላይ ትምህርትና ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ስልጠናዊ ውይይቱ ከአመራሩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው መሆኑን ገልጸው፥ ውሳኔዎችን ስናሳልፍና ጉዳዮችን ስናስፈጽም ከጥቅም ግጭት የጸዱ መሆናቸውን መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል።...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 18/2018 ዓ.ም) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ) በኢትዮጵያ ከህንድ አምባሳደር ጋር በፀረ-ሙስና ትግል ማጎልበትና ትብብር ሥራዎች ላይ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ በኢትዮጵያ የህንድ ኢንቨስተሮች የቢዝነስ ከባቢ ምቹ እና የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ከሙስና የፀዳ ከማድረግ አንጻር ያለውን ምልከታ የጋራ ማድረግ ተችሏል። በሌላ በኩል የፀረ-ሙስና ትግልን ከማጠናከር አንጻር በሁለቱ አገሮች መካከል...
Read More
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ የካቲት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ‘‘የከፍተኛ አመራሩ አርዓያነት፣ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ፋይዳ’’ በሚል መሪ ቃል ዘርፍ-ተኮር ስልጠናዊ ውይይት አካሂዷል። ስልጠናዊ ውይይቱ ከፍተኛ አመራሩ ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያለው ሚና የጎላ በመሆኑ በዘርፉ የሙስና ሥጋት እና ተጋላጭነትን በመለየት የጋራ መግባባት መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ...
Read More
1 2 3